ዋና ገጽ   የመጽሐፍ ቅዱስ ቃላት መፈለጊያ   ትምህርቶች   የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች   የነጻ መዝሙሮች   ነጻ ዳውንሎድ   ያግኙን 
website search (GO!)
 
ዋና ገጽ » የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች » ኤፌሶን » ጥናት 1 (ኤፌሶን 1፣1-3)
Email this page to a friend Printer-friendly   Friday, 3 February 2012
ዋና ገጽ
የመጽሐፍ ቅዱስ ቃላት መፈለጊያ
የመጽሐፍ ቅዱስ ማውጫ
የዕለቱ የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ
አዮታ ሶፍትዌር
ትምህርቶች
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች
የነጻ መዝሙሮች
ነጻ ዳውንሎድ
ያግኙን Contact us
ጥያቄ መጠያየቂያ Q&A
የእገዛ ገጽ Help

“እኔ ግን ለኃይልህ እቀኛለሁ በምሕረትህም ማልዶ ደስ ይለኛል በመከራዬ ቀን መጠጊያዬና አምባዬ ሆነኸኛልና።“
(መዝሙረ ዳዊት 59:16)

rss

Today's verse

ጥናት 1 (ኤፌሶን 1፣1-3)

pdf version

የመልእክቱ ጸሐፊ ጳውሎስ መሆኑን ራሱ መልእክቱ ይገልጻል (1፣1; 3፣1):: ጳውሎስ የቆላስይስን መልእክት በጻፈበት ጊዜ፣ በ60 ዓ.ም. ገደማ በሮም እስር ላይ እያለ ይህን ደብዳቤ እንደጻፈው ይታመናል (3፣1 4፣1 6፣20 ሐዋ 28፣30):: ይህ መልእክት ኤፌሶንን ጨምሮ ወደ ሌሎች ከተሞችም እንዲደርስ የተጻፈ ዘዋሪ ደብዳቤ ሳይሆን አይቀርም:: ምክንያቱም በጥንታዎ ብራናዎች ላይ “በኤፌሶን ላሉት” 1፣1 የሚለው ስንኝ አይገኝም:: ከዚህም በተጨማሪ ጳውሎስ እንደ ሌሎቹ መልእክቶች የስዎችን ስም እየጠራ ሰላምታ አያቀርብም፣ በዚያች ቤ/ክ ብቻ ስለሚገኝ የተለየ ችግር ወይም ሁኔታ አያነሳም፣ በተጨማሪም ትምህርቱ ሁሉ ሁሉንም አብያተ ክርስቲያናት እንዲመለከት ተደርጎ የቀረበ ነው:: በዚህ መልእክት “ቤተ ክርስቲያን” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የአጥቢያን ቤ/ክ ሳይሆን አጠቃላይዋን ቤ/ክ (universal church) ነው::


 

ሀ)ሰላምታ ቁ. 1-3

 

·       በእግዚአብሔር ፈቃድ ሐዋርያ መሆን

·       በሰው ፈቃድ ወይም በቤ/ክ ፈቃድ ወይም በራስ ፈቃድ ሳይሆን፣ በእግዚአብሔር ፈቃድ ብቻ (ገላ 1፣10-17)

 

·       ሐዋርያ:- በዚህ ክፍል አላማችን ስለ ሐዋርያት አገልግሎት መሉ ጥናት ለማካሄድ ሳይሆን የሐዋርያን ምንነት ጳውሎስ ሊያስተላልፈው ከፈለገው ሃሳብ ጋር ለማገናዘብ ነው:: የሐዋርያትን አገልግሎት በምዕራፍ 4 በይበልጥ እንመለከታለን::

 

·       የተላከ መልእክተኛ ማለት ነው::

·       ላኪው የላከው እንጂ በራሱ ተነሳሽነት የማይሄድ

·       ላኪው መልእክት አደራ ብሎ የሰጠው እንጂ የራሱ መልእክት ያልሆነ

·       ላኪው የሚያስፈልገውን ትጥቅ፣ ብቃትና ስልጣን የሰጠው እንጂ በቂ ነገር ያልታጠቀ ወይም በራሱ ወይም በስዎች ስልጣንና ትጥቅ የሚሄድ አይደለም

·       ሐዋርያነቱን ማሳወቁ አብያተ ክርስቲያናቱ ሥልጣኑን አውቀው የሚያስተላልፈውም መልእክት ከእግዚአብሔር እንደሆነ ተረድተው እንዲታዘዙ ለማድረግም ነው:: መልእክቱን ቢቃወሙ ሐዋርያን ስለሚቃውሙና ሐዋርያንም መቃወም ጌታን መቃወም ስለሆነ::

 

·       የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ

·       የክርስቶስ አገልጋይና መልእተኛ እንጂ የሰው አገልጋይና መልእተኛ ያልሆነ:: ጌታውን እንጂ ሰውን ደስ ለማሰኘት ያልቆመ::

 

·       ቅዱሳንና ምእመናን

·       ቅዱስ:- በዚህ ክፍል አላማችን ቅዱስ የሚለውን ቃል ጠቅላላ ትርጉም ለማጥናት ሳይሆን የቃሉን መሠረታዊ ትርጉም ለመያዝና አማኞች በጌታ የተቀደሱ ወይም ቅዱሳን እንደሆኑ ለማየት ነው::

 

·       ከሌሎች ሁሉ የተለየ (ልዩ)

·       ይሄውም በክብሩና በግርማው፣ በኃያልነቱና በታላቅነቱ ወዘተ በነገር ሁሉ ተመሳሳይ ወይም ተቀራራቢ የሌለው እግዚአብሔር ነው:: ራእይ 4፣8 ኢሳ 6፣3

·       ከእግዚአብሔር የተነሳ አንዳንድ ነገሮች ከእርሱ ጋር ካላቸው የቅርብ ግንኙነት የተነሳ ቅዱስ ይባላሉ::

·       ቦታ ዘጸ 3፣5

·       ተራራ 2ጴጥ 1፣18

·       ቤተ መቅደስ ሐዋ 6፣13 ዕብ 9፣1-3/9፣24-25

·       ኢየሩሳሌም ከመቅደሱ የተነሳ ማቴ 4፣5/27፣53

·       ወዘተ

 

·       ንጹህ መሆንና አለመቆሸሽን (አለመርከስን) ያመለክታል 1ጴጥ 1፣15-16

·       በኢየሱስ ያመኑ ሁሉ እንደተቀደሱ (ቅዱስን እንደሆኑ) መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምራል ሮሜ 15፣16 1ቆሮ 1፣30-31/6፣11 2ተሰ 2፣13 ዕብ 10፣10 1ጴጥ 1፣2

 

·       ምእመናን

·       ምእመናን ወይም በሌሎች ትርጉሞች (ለታመኑ/faithful) የሚለው እነዛኑ አማኞች ለመጥራት የተጠቀመበት አባባል ነው::

 

·       ጸጋና ሰላም

·       ጸጋና ሰላም የሚለው እዚህ ላይ በተለይ ለሰላምታ የተጠቀመው እንጂ የጸጋን መንፈሳዊ ትርጉም ሁሉ ለማመልከት አይደለም:: ጳውሎስ ይህንን ሰላምታ በሁሉም መልእቶቹ ላይ ተጠቅሞባቸዋል:: ጸጋ በግሪኮች ዘንድ የተለመደ ሰላምታ ሲሆን፣ ሰላም (shalom) ደግሞ የአይሁዶች ሰላምታ ነው::

 


 

ለ)የመንፈስዊ በረከቶች አይነት፣ ብዛትና ስፍራ ቁ. 3

 

ማሳሰቢያ ለቁርጥ 3:- ይህንን ስፍራ ስናጠና አላማችን መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጻፉትን በረከቶች ሁሉ ለመዘርዘር ሳይሆን በዚህ በኤፌሶን መልእክት ላይ የተዘረዘሩትን መንፈስዊ በረከቶች ለማየትና፣ ጸሐፊው ሊያስተላልፍ የፈለገውን ሃሳብ በትክክል ለመረዳት ነው:: እዚህ ክፍል ላይ ልብ ማለት ያለብን፣ በረከቶቹ በአይነትና በቦታ የተውሰኑ መሆናቸውን ነው::

 

·       የበረከቱ አይነትና ብዛት

·       መንፈሳዊ

·       መንፈሳዊ የሚለው የሥጋዊ ተቃራኒ ነው ወይም ሥጋዊ ያልሆነ ማለት ነው::

·       በቀድሞው ኪዳን ሕግን በመጠበቅ ከሚገኘው የእስራኤል በረከት የተለየ ዘዳ 28፣1-6/28፣11

·       ሁሉ (every spiritual blessing)

·       የቀረ መንፈሳዊ በረከት የለም ወይም መንፈሳዊ በረከቶች በሙሉ ያለ መቆጠብ (without reservation)

 

·       የበረከቱ ቦታ/ስፍራ/ክልል/ወሰን/sphare

·       በሰማያዊ ስፍራ (heavenly places)

·       የቃሉ ትርጉም

·       ይህ ስንኝ በዚህ መልእክት ውስጥ 5 ጊዜ ተጠቅሷል 1፣3/ 1፣20-21/ 2፣6-7/ 3፣10/ 6፣12:: እነዚህን ቦታዎች በጥንቃቄ ስንመረምር የሚከተሉትን ሃሳቦች እናገኛለን:-

·       ክርስቶስን እግዚአብሔር በሰማያዊ ስፍራ በቀኙ እንዳስቀመጠው 1፣20-21

·       እኛንም እግዚአብሔር ከክርስቶስ ጋር በሰማያዊ ስፍራ እንዳስቀመጠን 2፣6-7

·       በመንፈሳዊ ስፍራ አለቆችና ስልጣናት እንዳሉ 3፣10

·       በመንፈሳዊ ስፍራ የክፋት መንፍሳዊ ሠራዊቶች እንዳሉ 6፣12

·       ከነዚህ ጥቅሶች የምንረዳው እንግዲህ ጳውሎስ “መንፈሳዊ ስፍራ” ብሎ የሚናገረው የማይታየውን አለም በሙሉ (የእግዚአብሔርን ማድሪያንም የክፉ መናፍስት መኖሪያንም) ሁሉ መሆኑን ነው::

 

·       በብሉይ ኪዳን የሚገኘው ሥጋዊ በረከት የሚሰጥበት ቦታ የከነዓን ምድር እንደሆነ (ዘዳ 28፣11)፣ በዚህ ክፍል ደግሞ መንፍሳዊ በረከት የሚገኘው በሰማያዊ ስፍራ ነው::

·       “እኛ አገራችን በሰማይ ነውና...” ፊል 3፣20

·       “...ለእናንተ በሰማይ መዝገብ ሰብስቡ...” ማቴ 6፣19-21

·       “...በላይ ያለውን እሹ፣ በላይ ያለውን አስቡ...” ቆላ 3፣1-2

·       “...ሕይወታችሁም በእግዚአብሔር ከክርስቶስ ጋር ተሰውሮአልና...” ቆላ 3፣3-4

·       “...በሰማይ ከተዘጋጀላችሁ ተስፋ የተነሳ...” ቆላ 1፣3-5

·       “...ይህ ርስት...ለእናንተ በሰማይ ቀርቶላችኋል::” 1ጴጥ 1፣3-5

 

·       አምላክና አባት

·       ኢየሱስ ሙሉ ሰው የሆነው አምላክነቱን ትቶ ነው (ፈል 2፣6-8):: እንደ ሙሉ ሰውነቱ አብ አምላኩ ነው:: ክርስቶስ ሙሉ ሰው፣ ሙሉም አምላክ ነውና::

·       በብሉይ ኪዳን እውነተኛውን የሰማይና የምድር ፈጣሪ አምላክ ከሌሎች አማልክት ለይቶ ለመጥራት የአብርሃም አምላክ ወይም የእስራኤል አምላክ ወዘተ ተብሎ እንደሚጠራ ጳውሎስም እውነተኛውን አምላክ ለማመልከት የተጠቀመበት ነው::

 

·       ምስጋና

·       የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ

·  እግዚአብሔር ከታላቅ ፍቅሩ የተነሳ ምንም ሳያስቀር በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ ስለባረከን ጳውሎስ ይህንን ክፍል ሲጽፍ በምስጋና ልብ ሆኖ ነው::


“ልጄ ሆይ፥ ሕጌን አትርሳ፥ ልብህም ትእዛዛቴን ይጠብቅ። ብዙ ዘመናትና ረጅም ዕድሜ ሰላምም ይጨምሩልሃልና።“
(መጽሐፈ ምሳሌ 3:1-2)

rss

Today's proverb

የኒውስ ሌተር ምዝገባ
የእርስዎ ስም ኢሜል አድራሻዎ ኢሜል አድራሻዎ (በድጋሚ)
»የመጽሐፍ ቅዱስ ቃላት መፈለጊያ   የመጽሐፍ ቅዱስ ቃላት መፈለጊያ
Copyright © 2004-2012 by iyesus.com
Terms of use | Contact us