ዋና ገጽ   የመጽሐፍ ቅዱስ ቃላት መፈለጊያ   ትምህርቶች   የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች   የነጻ መዝሙሮች   ነጻ ዳውንሎድ   ያግኙን 
website search (GO!)
 
ዋና ገጽ » የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች » ኤፌሶን » ጥናት 3 (ኤፌሶን 1፣3-14 ለ) መንፈሳዊ በረከቶች - ክፍል 2
Email this page to a friend Printer-friendly   Friday, 3 February 2012
ዋና ገጽ
የመጽሐፍ ቅዱስ ቃላት መፈለጊያ
የመጽሐፍ ቅዱስ ማውጫ
የዕለቱ የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ
አዮታ ሶፍትዌር
ትምህርቶች
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች
የነጻ መዝሙሮች
ነጻ ዳውንሎድ
ያግኙን Contact us
ጥያቄ መጠያየቂያ Q&A
የእገዛ ገጽ Help

“እኔ ግን ለኃይልህ እቀኛለሁ በምሕረትህም ማልዶ ደስ ይለኛል በመከራዬ ቀን መጠጊያዬና አምባዬ ሆነኸኛልና።“
(መዝሙረ ዳዊት 59:16)

rss

Today's verse

ጥናት 3 (ኤፌሶን 1፣3-14 ለ) መንፈሳዊ በረከቶች - ክፍል 2

pdf version

ማሳሰቢያ:- መንፈሳዊ በረከቶች ብለን በሰየምነው በዚህ ጥናት ውስጥ በዝርዝር ልናይ የምንፈልገው መንፈሳዊ በረከቶቹን ብቻ ነው:: ይህም ማለት በረከቶቹን በማን በኩል እንደተባረክንና ይህንንስ ለማድረግ እግዚአብሔርን ያነሳሳው (motive) ምን እንደሆነ አሁን አንመለከትም:: እነዚህን ነገሮች በኋላ ላይ እንመለከታቸዋለንና::

 

1.              በዚህ ክፍል ውስጥ የሚከተሉት መንፈሳዊ በረከቶች ተዘርዝረዋል:-

1.    አለም ሳይፈጠር መረጠን

2.    አስቀድሞ ወሰነን (የእርሱ ልጆች እንሆን ዘንድ)

3.    ቤዛነትና የበደል ስርየት አገኘን

4.    ጸጋውን አበዛልን/አትረፈረፈልን

·       በጥበብና በአእምሮ ሁሉ

·       የፈቃዱን ምስጢር አስታወቀን

5.    ርስትን ተቀበልን

6.    በመንፈስ ቅዱስ ታተምን

 

ማሳሰቢያ:- ከዚህ በላይ ከተዘረዘሩት በረከቶች ውስጥ በዚህ በክፍል 2 ደግሞ ከ4-6 ያሉትን እንመለከታቸዋለን::

 

2.              ጸጋውን አበዛልን/አትረፈረፈልን

 

·       ሀ) ጸጋውን አበዛልን

·       ጸጋ

ተቀባዩ የማይገባው ሆኖ ሳለ ሰጪው በበጎ ፈቃዱ በነጻ የሚሰጠው ስጦታ፣ እንዲያው የሚያደርገው ቸርነትና መልካም ሥራ:: ከሥራ የሚገኝ ነገር ሁሉ ለሠራው ሰው ደመወዙ፣ ለአሠሪው ደግሞ ሊከፍለው የሚገባ ዕዳ እንጂ ጸጋ አይደለም (ሮሜ 4፣4):: ጸጋ የሚለው ቃል በአዲስ ኪዳን በተለይ ሰው ከሰው ጋር ያለውን ግንኙነት የሚያመለክት ሳይሆን፣ እግዚአብሔር በበጎ ፈቃዱ እንዲያው በነጻ ያደረገልንና የሰጠንን ስጦታ ሁሉ የሚያመለክት ነው:: እዚህ ላይ ልብ ማለት የሚገባን ነገር ቢኖር፣ ነጻ የሆነና ምንም ሳይከፈልበት የሚገኝ ነገር ሁሉ ብዙ ጊዜ ርካሽ የሆነን ነገር ነው የሚያሳየው:: በክርስቶስ የተሰጠን የእግዚአብሔር ነጻ ስጦታ ወይም ጸጋ ግን፣ በምንም ዋጋ ሊከፈል የሚችል ያልሆነ፣ ነፍሳችንን እንኳን ብንሰጥ የማይበቃ፣ በምድር ላይ ያለ ነገር ሁሉ ተሰብስቦ ሊገዛው የማይችል ነው:: ዋጋ የማይገኝለት ውድነቱ ራሱ እግዚአብሔር ለእኛ በነጻ እንዲሰጠን ካደረገው አንዱ ምክንያት ነው:: 1 ጴጥ 1፣18-19

 

·       ማብዛት (abound)

ከሚያስፈልገው ወይም ከሚበቃው በላይ መጨመር፣ ማትረፍረፍ፣ ማባከን

 

 

የእግዚአብሔር ጸጋ የሚያድን ብቻ ወይም የበደል ይቅርታ የሚያስገኝ ብቻ ወይም ከፍርድ የሚያስመልጥ ጸጋ ብቻ አይደለም፣ ነገር ግን የተትረፈረፈ ጸጋ እንጂ:: ከማዳንና ከይቅርታ በላይ የዘላለምን ክብር፣ ልጅነትና ርስትን ከጥበብና ከአእምሮ ሁሉ ጋር የሚጨምር፣ ከበቂ በላይ የሆነ የተትረፈረፈ ጸጋ ነው:: ለሰው ልጆች የኃጢአት ይቅርታና ምሕረት ራሱ በቂ ነበርና::

 

በሉቃ 15፣11-32 ላይ ባለው የጠፋው ልጅ ታሪክ ላይም የምንመለከተው ተመሳሳይ የእግዚአብሔርን ጸጋና ምሕረት ነው:: ለጠፋው ልጅ እንደ ሌሎቹ የአባቱ ባሪያዎች መሆን ብቻ በጣም በቂው ነበር:: ቢበዛ ቢበዛ ደግሞ የአባቱን ምሕረት አግኝንቶ የተማረ ልጅ መሆን ብቻ ራሱ ትልቅ ነገር ነው:: አባቱ ግን ከነቆሻሻው ከማቀፍ ጀምሮ፣ አዲስ ልብስንና ቀለበትን እንዲሁም በቤት ለነበረው ልጅ እንኳን አድርጎ የማያውቀውን ታላቅ ድግስ አደረገለት:: ይህም አባቱ ልጁን እንዲያው ይቅር ብቻ ብሎ በዚያ ብቻ ሊያበቃ እንዳልወደደና ምሕረቱና ጸጋው፣ ፍቅሩም የተትረፈረፈ እንደ ሆነ ያሳየናል::

 

·       ለ) በጥበብና በአእምሮ ሁሉ

·       ጥበብ

ጥበብ የሚለው ቃል በተለያዩ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ውስጥ በተለያየ ሁኔታ ስለተገለጠ፣ የቃሉን ፍቺ እንደ ምንባቡና እንደ ክፍሉ መረዳት ይገባል::

እንደ ጳውሎስ አገላለጽ፣ ጥበብ ማግኘት ማለት ከዘመናት በፊት በክርስቶስ ተሰውሮ የነበረው የእግዚአብሔር የማዳን እቅድን ወይም ፕላንን በሙላት ማወቅና መረዳት ነው::

“...እግዚአብሔር አስቀድሞ ከዘመናት በፊት ለክብራችን የወሰነውን፣ ተሰውሮም የነበረውን የእግዚአብሔርን ጥበብ በምስጢር እንናገራለን::” 1ቆሮ 2፣6-7

“...የእግዚአብሔርን ምስጢር እርሱንም ክርስቶስን እንዲያውቁ እጋደላለሁ፣ የተሰወረ የጥበብና የእውቀት መዝገብ ሁሉ በእርሱ ነውና::” ቆላ 2፣2-3

“...ከእግዚአብሔር ዘንድ ጥበብና ጽድቅ ቅድስናም ቤዛነትም በተደረገልን በክርስቶስ የሆናችሁ ከእርሱ ነው:: ” 1ቆሮ 1፣30

 

በዚህም ክፍል ጥቂት ወረድ ብሎ በኤፌ 1፣9 ላይ “በክርስቶስ ለማድረግ እንደ ወደደ እንደ አሳቡ፣ የፈቃዱን ምስጢር አስታውቆናልና” ይላል:: ስለዚህ በዚህ ክፍል አገላለጽ ጥበብ የሚለው እንግዲህ የእግዚአብሔር የፈቃዱን ምስጢር ማወቅን፣ እግዚአብሔር በክርስቶስ ለማድረግ ያሰበውን ዘላለማዊ ፈቃዱን መረዳት ነው::

 

·       አእምሮ

ማስተዋል፣ መረዳት፣ ማገናዘብ፣ ማመዛዘን፣ ማጤን ወዘተ

 

እግዚአብሔር እንግዲህ ከመዳንና ከይቅርታ በላይ በክርስቶስ ያለውን የእርሱን ጥበብ እንድናስተውልና እንድንረዳ፣ በመረዳትም ባለጠጎች እንድንሆን ይወዳል ማለት ነው:: የሰማያዊ ምስጢር መረዳት ድሆች እንድንሆን የእግዚአብሔር አላማ አይደለም::

 

 

·       ሐ) የፈቃዱን ምስጢር አስታወቀን

·       ምስጢር

ምስጢር ማለት:- ያለ፣ ነገር ግን ለሁሉም ያልታወቀ ወይም ያልተገለጠ ጉዳይ ማለት ነው:: ከዘመናት በፊት በእግዚአብሔር ብቻ ይታወቅ የነበረ አሁን ግን ለእኛ የተገለጠ:: ምስጢር ለቀረቡና ለታመኑ ወዳጆች የሚገለጥ ጉዳይ ነው:: እግዚአብሔርም ምስጢሩን ለእኛ ከመግለጡ በፊት እኛን ወደ እርሱ ማቅረብ ነበረበት:: ስለዚህ እግዚአብሔር የሚመቸውን ጊዜ ጠብቆ ነው ማለት ነው ምስጢሩን

የገለጸው::

 

·       የዘመን ፍጻሜ

መጽሐፍ ቅዱስ የዘመን ፍጻሜ ብሎ የሚጠራው ክርስቶስ ወደ አለም ከመጣበት ጊዜ አንስቶ ያለውን ዘመን ነው:: ዕብ 1፣2 1ጴጥ 1፣20

 

·       የእግዚአብሔር አሳብ/ፈቃድ

·       በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ መጠቅለል

በእንግሊዘኛው:- head up, sum up, bring together, unify etc in christ.

በአማርኛ:- ጠቅልሎ መግዛት፣ አንድ አድርጎ መግዛት ወይም በክርስቶስ አገዛዝ፣ ራስነት፣ ሥልጣን ሥር መሰብሰብ፣ ማያያዝ፣ አንድ ማድረግ፣ ማገጣጠም፣ ማቀራረብ፣ ማዋሃድ፣ ማስማማት ወዘተ

 

እዚህ ላይ እንግዲህ ልብ ልንል የሚገባው የእግዚአብሔር ዘላለማዊ እቅድና አላማ:-

1.             በምድር እና በሰማይ ያሉትን ሁሉ በክርስቶስ ራስነት ወይም ስልጣን ሥር ማድረግ ፊል 2፣9-11 ማቴ 28፣18

 

2.             እርስ በርስ ማዋሃድ፣ ማስማማት፣ አንድ ማድረግና ሰላምን መፍጠር ነው:: በክርስቶስ ራስነት ሥር የሆነ ሰላምና መስማማት (harmony) እንግዲህ አንዱ የእግዚአብሔር ዋነኛው ዘላለማዊ እቅዱ ነው:: አይሁድ ከአሕዛብ፣ ባሪያና ጨዋ፣ ሴትና ወንድ፣ ወዘተ ገላ 3፣28 ኤፌ 1፣11-17

 

 


 

3.              ርስትን ተቀበልን

·        ርስት

ርስት ብሎ እዚህ ላይ የጠቀሰው፣ ውርስን ለማመልከት ነው::

ከመዳን ባሻገር የምንወርሰው የዘላለም ርስት እግዚአብሔር እንዳዘጋጀልን መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል::

“ልጆች ከሆንን ወራሾች ደግሞ ነን፣ ማለት የእግዚአብሔር ወራሾች ነን...” ሮሜ 8፣17

የማይጠፋ፣ እድፈትም የሌለበት፣ የማያልፍና በሰማይ የተዘጋጀ ርስት 1ጴጥ 1፣3-5

ርስት ምንም እንኳን የተሰጠንና የተዘጋጀልን ቢሆንም ሙሉ በሙሉ የምንወርሰው ግን ወደፊት ነው:: ስለዚህ ርስት የቅዱሳን ተስፋ ነው:: እግዚአብሔር ለደህንነት ብቻ አልጠራንምና ነገር ግን ለርስትና ለታላቅም ተስፋ እንጂ::

 

 

4.              በመንፈስ ቅዱስ ታተምን

·       ማኅተም

የባለቤትነት ምልክትና የእውነተኝነት ማረጋገጫ ሲሆን፣ ከማኅተም ጀርባ አንድ ሥልጣን እንዳለ ያሳያል::

 

·       መያዣ

ቀብድ (down payment)፣ እዚህ ላይ ሰለ መያዣ ወይም ስለ ቀብድ ሲናገር ሰለ ግማሽ ዋጋ ለመናገር ሳይሆን በተለይ መያዣነትን፣ ማረጋገጫነትንና ዋስትናን ለማሳየት ነው:: ስለዚህ እግዚአብሔር እንግዲህ መያዣ የሰጠን፣ ርስት ወይም ውርስ እንዳዘጋጀልንና ይህንንም ርስት በርግጥ እንደምናገኝ ለማረጋገጥና ዋስትና ለመስጠት ነው:: በሮሜ 8፣23 ላይ “የመንፈስ በኩራት ያለን” የሚለው ቃል፣ የመንፈስ የመጀመሪያ ስጦታ፣ ሊመጣ ላለው ለዋናው ስጦታ ቅምሻ ማለት ነው:: ስለዚህም እዚህ ቦታ መንፈስ ቅዱስ፣ የተስፋው መንፈስ ተብሎ ይጠራል::

ሌላው እዚህ ላይ ልብ ልንለው የሚገባን ነገር፣ ይህንን መያዣ የሰጠን እግዚአብሔር እንጂ እኛ ለእግዚአብሔር የሰጠነው አይደለም:: ስለዚህ በዚህ ክፍል ጳውሎስ መያዣ የሚለውን ቃል፣ እኛ መዳናችንን ለመፈጸም የሚቀረንን ሩጫ ለማመልከት የተጠቀመበት አይደለም::

 


“ልጄ ሆይ፥ ሕጌን አትርሳ፥ ልብህም ትእዛዛቴን ይጠብቅ። ብዙ ዘመናትና ረጅም ዕድሜ ሰላምም ይጨምሩልሃልና።“
(መጽሐፈ ምሳሌ 3:1-2)

rss

Today's proverb

የኒውስ ሌተር ምዝገባ
የእርስዎ ስም ኢሜል አድራሻዎ ኢሜል አድራሻዎ (በድጋሚ)
»የመጽሐፍ ቅዱስ ቃላት መፈለጊያ   የመጽሐፍ ቅዱስ ቃላት መፈለጊያ
Copyright © 2004-2012 by iyesus.com
Terms of use | Contact us