ዋና ገጽ   የመጽሐፍ ቅዱስ ቃላት መፈለጊያ   ትምህርቶች   የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች   የነጻ መዝሙሮች   ነጻ ዳውንሎድ   ያግኙን 
website search (GO!)
 
ዋና ገጽ » የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች » ኤፌሶን » ጥናት 4 (ኤፌሶን 1፣3-14 ሐ) ሠራተኞችና አማኞች
Email this page to a friend Printer-friendly   Friday, 3 February 2012
ዋና ገጽ
የመጽሐፍ ቅዱስ ቃላት መፈለጊያ
የመጽሐፍ ቅዱስ ማውጫ
የዕለቱ የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ
አዮታ ሶፍትዌር
ትምህርቶች
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች
የነጻ መዝሙሮች
ነጻ ዳውንሎድ
ያግኙን Contact us
ጥያቄ መጠያየቂያ Q&A
የእገዛ ገጽ Help

“እኔ ግን ለኃይልህ እቀኛለሁ በምሕረትህም ማልዶ ደስ ይለኛል በመከራዬ ቀን መጠጊያዬና አምባዬ ሆነኸኛልና።“
(መዝሙረ ዳዊት 59:16)

rss

Today's verse

ጥናት 4 (ኤፌሶን 1፣3-14 ሐ) ሠራተኞችና አማኞች

pdf version

ማሳሰቢያ:- በዚህ ክፍል ውስጥ ለማየት የምንሞክረው፣ በጥናታችን ክፍል ውስጥ  የተጠቀሱትን ስብዕት/persons እና መንፈሳዊ በረከቶቹ ወደ እኛ እንዲደርሱ እነርሱ ያበረከቱትን የሥራ ድርሻ ነው:: ይሄም ማለት ለማየት የምንሞክረው በዚህ በጥናታችን ክፍል ውስጥ የተዘረዘሩትን ሥራዎቻቸውን እንጂ፣ በመጽሐፍ ቅዱስ ሁሉ የተጠቀሱትን አይደለም::

 

በዚህ በጥናታችን ክፍል ውስጥ 4 አይነት ስብዕት/persons እና ለመንፈሳዊ በረከቶቹም እውን መሆን፣ እነዚህ ስብዕት/persons ያበረከቱት ሥራ ተገልጾአል:-

 

1.              አብ

·       ሀ)የአብ የሥራ ድርሻ

1.                  መንፈሳዊ በረከቶቹ ሁሉ ከእርሱ ነው የመጡት ወይም የመንፈሳዊ በረከቶቹ ሁሉ ምንጭና ባራኪ አብ ነው::

·       “...በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ::” ኤፌ 1፣3

·       “...በክርስቶስ መረጠን::” ኤፌ 1፣4

·       “...ለእርሱ ልጆች ልንሆን አስቀድሞ ወሰነን::” ኤፌ 1፣5

·       “ጸጋውንም በጥበብና በአእምሮ ሁሉ አበዛልን::” ኤፌ 1፣8

·       “...የፈቃዱን ምሥጢር አስታውቆናልና...” ኤፌ 1፣9

 

2.                  በክርስቶስ ለተሠሩት ሥራዎች ሁሉ እቅድና ፕላን አውጪ አብ ነው:: የተጠቀሱትም መንፈሳዊ በረከቶች ሁሉ እውን የሆኑት እንደ እርሱ አሳብና ፈቃድ ነው::

·       “በክርስቶስ ለማድረግ እንደወደደ እንደ አሳቡ...” ኤፌ 1፣9

·       “...በዘመን ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ ያለው አሳቡም...” ኤፌ 1፣10

·       “እንደ ፈቃዱ ምክር ሁሉን የሚሠራ እንደ እርሱ አሳብ...” ኤፌ 1፣11

 

·       ለ)አብ ከላይ የተጠቀሱትን ሥራዎች እንዲያከናውን ያነሳሳው ነገር (motive)

1.                  ፍቅር ኤፌ 1፣4:: በድሮው የአማርኛ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም “በፍቅር” የሚለው ቃል እኛ በፍቅር እንድንሆን የሚለውን ትርጉም የሚይዝ ቢያስመስልም፣ በኦርጂናሉ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ግን ይህ ቃል የአብን ፍቅር የሚያሳይ ነው:: ስለዚህም በአዲሱ መደበኛ ትርጉም በቁጥር 4-5 ላይ አብ በፍቅር እንደወሰነን ግልጽ ያደርገዋል:: “...በፍቅር፣ በኢየሱስ ክርስቶስ ልጆቹ እንሆን ዘንድ፣ እንደ በጎ ፈቃዱ አስቀድሞ ወሰነን”:: ስለዚህ እግዚአብሔር በመንፈሳዊ በረከቶች ሁሉ እንዲባርከን ያነሳሳው ዋና ነገር ፍቅር ነው::

 

2.                  ይህን ለማድረግ የአብ በጎ ፈቃድ ስለሆነ ወይም ይህንን ለማድረግ ስለወደደ

·       “በበጎ ፈቃዱ እንደወደደ...” ኤፌ 1፣5

·       “በክርስቶስም ለማድረግ እንደወደደ...” ኤፌ 1፣9

·       “እንደ ፈቃዱ ምክር ሁሉን የሚሠራ እንደ እርሱ አሳብ...” ኤፌ 1፣11

 

·       ሐ)አብ መንፈሳዊ በረከቶቹን የባረከበት ሁኔታ

·       ከእኛ በጎ ሥራ ወይም መልካምነት ሳይሆን ከጸጋው ብዛት ነው

·       “ዓለም ሳይፈጠር...” ኤፌ 1፣4

·       “...አስቀድሞ ወሰነን::” ኤፌ 1፣5

·       “...እንዲያው የሰጠን የጸጋው ክብር...” ኤፌ 1፣6

·       “...እንደ ጸጋው ባለጠግነት መጠን...” ኤፌ 1፣7

·       “ጸጋውንም ... አበዛልን::” ኤፌ 1፣8

 

·       መ)አብ መንፈሳዊ በረከቶቹን ሁሉ የባረከበት ምክንያት

·       “...እንዲያው የሰጠን የጸጋው ክብር ይመሰገን ዘንድ ይህን አደረገ::” ኤፌ 1፣6

·       በዚህ ክፍል ክብር የሚለው ጥሬ ቃል ትርጉሙ:- በሌሎች ዘንድ መመስገንን፣ መከበርን፣ መወደስን፣ መሞገስን፣ መደነቅን ወዘተ የሚያነሳሳ ማናቸውም መልካም ነገር ወይም የተለየ ነገር ወዘተ ነው::

·       ጸጋው የሚያድን ወይም የሚምር መሆኑ ራሱ አንዱ የጸጋው ክብር ነው:: ጸጋው ግን ከምህረትና ከይቅርታ ያለፈ የተትረፈረፈ፣ የልጅነት ስልጣን የሚሰጥ፣ ርስትን የሚያወርስ፣ ጥበብንና ማስተዋልን የሚሰጥ ወዘተ ነው:: እነዚም ነገሮች የጸጋው ክብር ናቸው::

·       “...እኛ ለክብሩ ምስጋና እንሆን ዘንድ ነው::” ኤፌ 1፣12

·       እዚህ ላይ የተጠቀሰውን አባባል በተለያየ ሁኔታ ልንረዳው እንችላለን:: በተለይ ግን በእኛ በሠራው ሥራ እግዚአብሔር በእኛም፣ በመላእክትም በፍጥረትም ሁሉ ክብሩ እንዲመሰገን ነው:: ይሄም እኛ ራሳችን የምስጋና ምክንያት እንድንሆን:: ራእይ 5፣8-14

·       “...ይህም ለክብሩ ምስጋና ይሆናል::” ኤፌ 1፣14

·       እግዚአብሔር በሠራው ሥራ ፍጥረት ሁሉ የእርሱን ጸጋ፣ መልካምነት፣ ምሕረት ወዘተ ወይም ክብር እንዲያመሰግኑ ነው::

 

ማጠቃለያ:- አብ የመንፈሳዊ በረከቶች ሁሉ ምንጭ እንዲሁም እቅድ አውጪ ነው:: ይህንን ሁሉ ያደረገውም ከፍቅሩና ከበጎ ፈቃዱ የተነሳ ነው:: በጎነቱ ስላነሳሳው፣ ጸጋው ብዙ ስለሆነ እንጂ ከእኛ ማንነትና መልካምነት አይደለም:: ስለዚህም እንዲያው ባደረገው ሥራ ሁሉ ክብሩንና ምስጋናውን ሊወስድ የሚገባው እርሱ ነው::

 

2.              ክርስቶስ/ወልድ

·       ሀ)መንፈሳዊ በረከቶች ሁሉ (በዚህ ክፍል የተጠቀሱት ስድስቱም በረከቶች በሙሉ) የተባረክነው በክርስቶስ (በክርስቶስ ውስጥ፣ በክርስቶስ አማካኝነት፣ በክርስቶስ ሥራ፣ በክርስቶስ በኩል ወዘተ) ነው::

·       “በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን...” ኤፌ 1፣3

·       “...በክርስቶስ መረጠን::” ኤፌ 1፣4

·       “...በኢየሱስ ክርስቶስ...ለእርሱ ልጆች ልንሆን አስቀድሞ ወሰነን::” ኤፌ 1፣5

·       “በውድ ልጁም እንዲያው የሰጠን ጸጋ...” ኤፌ 1፣6

·       “በውድ ልጁም...በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን እርሱም የበደላችን ስርየት::” ኤፌ 1፣7

·       “...በክርስቶስ ደግሞ ርስትን ተቀበልን::” ኤፌ 1፣11

·       “...በክርስቶስ አምናችሁ፣ በተስፋው መንፈስ በመንፈስ ቅዱስ ታተማችሁ...” ኤፌ 1፣13

 

·       ለ)ክርስቶስ የእግዚአብሔር ዘላለማዊ እቅድና ፕላን መፈጸሚያ ነው::

·       “በዘመን ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ ያለው አሳቡም፣ በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው::” ኤፌ 1፣10

 

ማጠቃለያ:- ይህ በክርስቶስ ወይም በልጁ ወዘተ የሚለው ቃል ከ10 ጊዜ በላይ በዚህ ክፍል ውስጥ ተጠቅሷል:: በዚህም፣ ምንም አይነት የእግዚአብሔር በረከት ከክርስቶስ ውጪ እንደሌለ ጸሐፊው ለማሳየት እንደፈለገ እንገነዘባለን:: እውነተኛው የወይን ግንድ ክርስቶስ ነውና (ዮሐ 15፣1-11):: በረከቱ ወደ ሰዎች እንዲመጣ ዋናው ቅድመ ሁኔታ የክርስቶስ የመስቀሉ ሥራ ነው:: እግዚአብሔር የአለምን ሩጫና የዘላለም ሃሳቡን የሚቋጨው በክርስቶስ ነው:: ይሄውም ሁሉም ከክርስቶስ ራስነት ስር ሲገዙ:: በዚህ ሁሉ ልንረዳ የሚገባን፣ አብ ለሰው ልጆች መፍትሔንና በረከትን ለማምጣት ያቀደውንና ያሰበውን ሁሉ የፈጸመው በክርስቶስ ነው:: እግዚአብሔር ጥንትም ቢሆን፣ አለማትንና ፍጥረታትን ለመፍጠር ሲያቅድ ይህን እቅዱን የፈጸመው ወይም ተግባራዊ ያደረገው በክርስቶስ ነበር (ዮሐ 1፣1-2 ዕብ 1፣1-2 ቆላ 1፣13-17):: ስለዚህ ክርስቶስ ማናቸውንም እቅዱን የሚፈጽምበት የእግዚአብሔር ጥበብና ዘዴ ነው:: ለዚህም ነው የእስራኤል ልጆች በበረሃ ጉዞአቸው በገጠማቸው ማናቸውም ችግር እንደ መፍትሄነት እግዚአብሔር የሚያመለክታቸው የነበረው ክርስቶስን ነበር (ዮሐ 3፣14-15 1ቆሮ 10፣4 ዮሐ 6፣31-35)::

 

3.              መንፈስ ቅዱስ

እግዚአብሔር ለእኛ ርስት እንዳዘጋጀልን የሚያረጋግጥ፣ የሚመሰክርና በረከቱን በሕይወታችን እውን እንዲሆን ወይም ለእኛ ሕይወት ትርጉም እንዲሰጥ ከሕይወታችን ጋር የሚያዛምድ ነው:: በዚህም ለእኛ ተስፋ የሚሰጠን ነው::

·       “...በተስፋው መንፈስ በመንፈስ ቅዱስ ታተማችሁ፣ እርሱም የርስታችን መያዣ ነው...” ኤፌ 1፣13-14

·       “የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ያ መንፈስ ራሱ ከመንፈሳችን ጋር ይመሰክራል::” ሮሜ 8፣16

 

ማጠቃለያ:- ያለ መንፈስ ቅዱስ ሥራ አብ በክርስቶስ የሠራው ሥራ ከእኛ ጋር አይዛመድም 1ቆሮ 12፣3:: የእግዚአብሔር ሥራ ከሕይወታችን ጋር ተዋሕዶ ለእኛ ትርጉም እንዲኖረው የሚያደርገው መንፈስ ቅዱስ ነው:: እርሱ ነው እግዚአብሔር የሠራልንንና ሊያደርግልን ያሰበውን ሥራ በሕይወታችን እውን በማድረግ እውነተኛ ተስፋ የሚሰጠን:: ያለ እርሱ እግዚአብሔር ያደረገልን ነገር ሁሉ ለእኛ ምንም ትርጉም አይሰጠንም::

 


 

4.              አማኞች

እግዚአብሔር የባረከን በረከት ወደ አማኞች እንዲመጣ የአማኞች ድርሻ፣ በክርስቶስ ማመን ወይም በእርሱ ተስፋ ማድረግ በቻ ነው::

·       “...በክርስቶስ...ተስፋ ያደረግን እኛ...” ኤፌ 1፣12

·       “እናንተም ደግሞ የእውነትን ቃል፣ ይኸውም የመዳናችሁን ወንጌል፣ ሰምታችሁ ደግሞም በክርስቶስ አምናችሁ...” ኤፌ 1፣13

 

እዚህ ላይ ልብ ልንል የሚገባው የአማኞች ዋና ድርሻ በክርስቶስ ማመን ነው:: እምነት ደግሞ ሥራ አይደለም ሮሜ 4፣1-5:: ይህ የጥናታችን ክፍል እንግዲህ በሥራና በእምነት ወይም በሠራተኞችና በአማኞች የተከፈለ ነው:: መንፈሳዊ በረከቶቹ ሁሉ ወደ እኛ እንዲደርሱ የሚያስፈልጉትን ሥራዎች ሁሉ አብ፣ ወልድና መንፈስ ቅዱስ ተከፋፍለውት እንመለከታለን:: ለአማኞች የቀረላቸው ድርሻ ቢኖር ሥራ ሳይሆን በክርስቶስ ላይ ያለ እምነት ነው:: ስለዚህ ጸሐፊው ደጋግሞ አብ ከበጎ ፈቃዱ፣ ከፍቅሩና ከማንነቱ የተነሳ ለክብሩ በክርስቶስ እንደባረከን በሰፊው ሲገልጽ የአማኞችን ድርሻ ግን በእምነት ላይ ብቻ ወስኖታል:: ይህም መንፈሳዊ በረከቶችን የተባረክነው ከእኛ ማንነትና ከመልካም ሥራችን ሳይሆን ከእግዚአብሔር ማንነትና ጸጋ የተነሳ መሆኑን ያስገነዝበናል:: አማኝ ሁሉ ከሁሉም በፊት በእግዚአብሔር ሥራ ላይ ማረፍ አለበት:: እግዚአብሔር ያለ እኛ ሥራና ያለ እኛ ማንነት እንደተቀበለንና እንደወደደን አምነን በእርሱ መልካምነት ላይ ልንደገፍ ይገባናል:: እግዚአብሔር እንዲቀበለን ከክርስቶስ መስዋዕት ሌላ ተጨማሪ መሥዋዕት፣ እግዚአብሔር ራሱ ከምህረቱ ከሠራልን ሥራ ሌላ ተጨማሪ የእኛ ሥራ አያስፈልግም:: በጌታ ከምንሮጠው ከማናቸውም ሩጫ በፊት ይህ ለሕይወታችን መሠረት ሊሆን ይገባል:: ክርስትና ከማረፍ፣ ከመወደድ እንዲሁም ከበረከት ነው የሚጀምረው::


“ልጄ ሆይ፥ ሕጌን አትርሳ፥ ልብህም ትእዛዛቴን ይጠብቅ። ብዙ ዘመናትና ረጅም ዕድሜ ሰላምም ይጨምሩልሃልና።“
(መጽሐፈ ምሳሌ 3:1-2)

rss

Today's proverb

የኒውስ ሌተር ምዝገባ
የእርስዎ ስም ኢሜል አድራሻዎ ኢሜል አድራሻዎ (በድጋሚ)
»የመጽሐፍ ቅዱስ ቃላት መፈለጊያ   የመጽሐፍ ቅዱስ ቃላት መፈለጊያ
Copyright © 2004-2012 by iyesus.com
Terms of use | Contact us