አንድ ጊዜ
ከዕውርነት
የፈወሰውን ሰው
ኢየሱስ እንዲህ ብሎ
ጠየቀው:- “...አንተ
በእግዚአብሔር ልጅ
ታምናለህን?...እርሱም
መልሶ:- ጌታ
ሆይ፣በእርሱ አምን
ዘንድ ማን ነው? አለ::
ኢየሱስም:-
አይተኸዋልም ከአንተ
ጋርም የሚናገረው
እርሱ ነው አለው::
እርሱም:- ጌታ ሆይ፣
አምናለው
አለ፣ሰገደለተም::“ዮሐ
9፣35-38
ሰዎች ሁሉ
የኢየሱስን ማንነት
ተረድተውና ክብሩንም
አይተው በእርሱ እንዲያምኑና
እንዲድኑ
የእግዚአብሔር ፈቃድ
ነው:: ስለዚህ ይህች
ጽሑፍ የኢየሱስን
ማንነት በጥልቀት
ለማወቅ፣“በእርሱ
አምን ዘንድ ማነው?“ ለሚሉ
ሁሉ የተዘጋጀች ናት::
አንተም
የእግዚአብሔርን ልጅ
ክብር አይተህ በእርሱ
እንድታምንና ለእርሱ
እንድትሰግድ
እግዚአብሔር
ይርዳህ::
ጽሑፏ
እግዚአብሔርን
በፍጹምና በቅን
ልባቸው ለማወቅና
ለመከተል ለሚፈልጉ፣
የእግዚአብሔርንም
እውነት ለተራቡና
ለተጠሙ የተዘጋጀች
ናት:: “ጽድቅን
የሚራቡና የሚጠሙ
ብፁዓን ናቸው
ይጠግባሉና::“ ማቴ 5፣6
አላማዋም ሰዎች
የአንድ ሃይማኖት
ተከታዮች እንዲሆኑ
ለማድረግ አይደለም::
ስለዚህም የትኛውንም
ሃይማኖት
አታንጸባርቅም::