| መዝሙረ ዳዊት 119 |
| 136 | ሕግህን አልጠበቅሁምና የውኃ ፈሳሽ ከዓይኖቼ ፈሰሰ። |
| 137 | አቤቱ፥ አንተ ጻድቅ ነህ፥ ፍርድህም ቅን ነው። |
| 138 | ምስክርህን በጽድቅ አዘዝህ፥ እጅግም ቅን ነው። |
| 139 | ጠላቶቼ ቃልህን ረስተዋልና የቤትህ ቅንዓት አቀለጠኝ። |
| 140 | ቃልህ እጅግ የነጠረ ነው፥ ባሪያህም ወደደው። |
| 141 | እኔ ታናሽና የተናቅሁ ነኝ ትእዛዛትህን ግን አልረሳሁም። |
| 142 | ጽድቅህ የዘላለም ጽድቅ ነው፥ ቃልህም እውነት ነው። |
| 143 | መከራና ችግር አገኙኝ ትእዛዛትህ ግን ተድላዬ ናቸው። |
| 144 | ምስክርህ ለዘላለም ጽድቅ ነው እንዳስተውል አድርገኝ፥ በሕይወትም አኑረኝ። |
| 145 | በፍጹም ልቤ ጮኽሁ፥ አቤቱ፥ ስማኝ ሥርዓትህን እፈልጋለሁ። |
| 146 | ወደ አንተ ጮኽሁ አድነኝ፥ ምስክርህንም እጠብቃለሁ። |
| 147 | ማለዳ ጮኽሁ ቃልህንም ተስፋ አድርጌአለሁ። |
| 148 | ቃልህን አስብ ዘንድ ዓይኖቼ ለመማለድ ቀደሙ። |
| 149 | አቤቱ፥ እንደ ቸርነትህ ድምፄን ስማ እንደ ፍርድህ ሕያው አድርገኝ። |
| 150 | በዓመፃ የሚያሳድዱኝ ቀረቡ፥ ከሕግህም ራቁ። |