| መዝሙረ ዳዊት 119 |
| 16 | በትእዛዝህ ደስ ይለኛል ቃልህንም አልረሳም። |
| 17 | ለባሪያህ መልካም አድርግ ሕያው እንድሆን፥ ቃልህንም እንድጠብቅ። |
| 18 | ዓይኖቼን ክፈት፥ ከሕግህም ተኣምራትህን አያለሁ። |
| 19 | እኔ በምድር እንግዳ ነኝ ትእዛዛትህን ከእኔ አትሰውር። |
| 20 | ነፍሴ ሁልጊዜ ፍርድህን እጅግ ናፈቀች። |
| 21 | ከትእዛዛትህ የሳቱትን ትዕቢተኞችንና ርጉማንን ዘለፍህ። |
| 22 | ምስክርህን ፈልጌአለሁና። ስድብንና ነውርን ከእኔ አርቅ። |
| 23 | አለቆች ደግሞ ተቀምጠው እኔን አሙኝ ባሪያህ ግን ሕግህን ያሰላስል ነበር። |
| 24 | ምስክርህም ተድላዬ ነው፥ ሥርዓትህም መካሪዬ ነው። |
| 25 | ነፍሴ ወደ ምድር ተጠጋች እንደ ቃልህ ሕያው አድርገኝ። |
| 26 | መንገድህን ነገርሁ ሰማኸኝም ሥርዓትህን አስተምረኝ። |
| 27 | የሥርዓትህን መንገድ እንዳስተውል አድርገኝ፥ ተኣምራትህንም አሰላስላለሁ። |
| 28 | ከኀዘን የተነሣ ነፍሴ አንቀላፋች በቃልህ አጠንክረኝ። |
| 29 | የዓመፅን መንገድ ከእኔ አርቅ፥ በሕግህም ማረኝ |
| 30 | የእውነትህን መንገድ መረጥሁ፥ ፍርድህንም አልረሳሁም። |