| መዝሙረ ዳዊት 119 |
| 91 | ሁሉም ባሪያዎችህ ናቸውና ቀኑ በትእዛዝህ ይኖራል። |
| 92 | ሕግህ ተድላዬ ባይሆን፥ ቀድሞ በጐስቍልናዬ በጠፋሁ ነበር። |
| 93 | በእርሱ ሕያው አድርገኸኛልና ፍርድህን ለዘላለም አልረሳም። |
| 94 | እኔ የአንተ ነኝ ፍርድህን ፈልጌአልሁና አድነኝ። |
| 95 | ኃጢአተኞች ያጠፉኝ ዘንድ ጠበቁኝ ምስክርህን ግን መረመርሁ። |
| 96 | የሥራህን ሁሉ ፍጻሜ አየሁ ትእዛዝህ ግን እጅግ ሰፊ ነው። |
| 97 | አቤቱ፥ ሕግህን እንደ ምን እጅግ ወደድሁ! ቀኑን ሁሉ እርሱ ትዝታዬ ነው። |
| 98 | ለዘላለም ለእኔ ነውና ትእዛዝህ ከጠላቶቼ ይልቅ አስተዋይ አደረገኝ። |
| 99 | ምስክርህ ትዝታዬ ነውና ካስተማሩኝ ሁሉ ይልቅ አስተዋልሁ። |
| 100 | ትእዛዝህን ፈልጌአለሁና ከሽማግሌዎች ይልቅ አስተዋልሁ። |
| 101 | ቃልህን እጠብቅ ዘንድ ከክፉ መንገድ ሁሉ እግሬን ከለከልሁ። |
| 102 | አስተምረኸኛልና ከፍርድህ አልራቅሁም። |
| 103 | ቃልህ ለጕሮሮዬ ጣፋጭ ነው ከማርና ከወለላ ይልቅ ለአፌ ጣፈጠኝ። |
| 104 | ከትእዛዝህ የተነሣ አስተዋልሁ ስለዚህ የሐሰትን መንገድ ጠላሁ። |
| 105 | ሕግህ ለእግሬ መብራት፥ ለመንገዴ ብርሃን ነው። |