| መጽሐፈ ምሳሌ 11 |
| 1 | አባይ ሚዛን በእግዚአብሔር ፊት አስጸያፊ ነው እውነተኛ ሚዛን ግን ደስ ያሰኘዋል። |
| 2 | ትዕቢት ከመጣች ውርደት ትመጣለች በትሑታን ዘንድ ግን ጥበብ ትገኛለች። |
| 3 | ቅኖች ቅንነታቸው ትመራቸዋለች ወስላቶችን ግን ጠማማነታቸው ታጠፋቸዋለች። |
| 4 | በቍጣ ቀን ሀብት አትረባም ጽድቅ ግን ከሞት ታድናለች። |
| 5 | የፍጹም ሰው ጽድቁ መንገዱን ያቀናለታል ኃጥእ ግን በኃጢአቱ ይወድቃል። |
| 6 | ቅኖችን ጽድቃቸው ይታደጋቸዋል ወስላቶች ግን በምኞታቸው ይጠመዳሉ። |
| 7 | ኀጥእ በሞተ ጊዜ ተስፋው ይቈረጣል፥ የኃያል አለኝታም ይጠፋል። |
| 8 | ጻድቅ ከጭንቀት ይድናል፥ ኀጥእም በእርሱ ፋንታ ይመጣል። |
| 9 | ዝንጉ ሰው በአፉ ባልንጀራውን ያጠፋል ጻድቃን ግን በእውቀት ይድናሉ። |
| 10 | በጻድቃን ልማት ከተማ ደስ ይላታል፥ በኀጥኣንም ጥፋት እልል ትላለች። |
| 11 | በቅኖች በረከት ከተማ ከፍ ከፍ ትላለች በኀጥኣን አፍ ግን ትገለበጣለች። |
| 12 | ወዳጁን የሚንቅ እርሱ አእምሮ የጐደለው ነው አስተዋይ ግን ዝም ይላል። |
| 13 | ለሐሜት የሚሄድ ምሥጢሩን ይገልጣል በመንፈስ የታመነ ግን ነገሩን ይሰውራል። |
| 14 | መልካም ምክር ከሌለ ዘንድ ሕዝብ ይወድቃል በመካሮች ብዛት ግን ደኅንነት ይሆናል። |
| 15 | ለማያውቅ የሚዋስ ክፉ መከራን ይቀበላል ዋስነትን የሚጠላ ግን ይድናል። |