| መጽሐፈ ምሳሌ 3 |
| 1 | ልጄ ሆይ፥ ሕጌን አትርሳ፥ ልብህም ትእዛዛቴን ይጠብቅ። |
| 2 | ብዙ ዘመናትና ረጅም ዕድሜ ሰላምም ይጨምሩልሃልና። |
| 3 | ምሕረትና እውነት ከአንተ አይራቁ በአንገትህ እሰራቸው በልብህ ጽላት ጻፋቸው። |
| 4 | በእግዚአብሔርና በሰው ፊትም ሞገስንና መልካም ዝናን ታገኛለህ። |
| 5 | በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ |
| 6 | በመንገድህ ሁሉ እርሱን እወቅ፥ እርሱም ጎዳናህን ያቀናልሃል። |
| 7 | በራስህ አስተያየት ጠቢብ አትሁን እግዚአብሔርን ፍራ፥ ከክፋትም ራቅ |
| 8 | ይህም ለሥጋህ ፈውስ ይሆንልሃል፥ ለአጥንትህም ጠገን። |
| 9 | እግዚአብሔርን ከሀብትህ አክብር፥ ከፍሬህም ሁሉ በኵራት |
| 10 | ጐተራህም እህልን ይሞላል፥ መጥመቂያህም በወይን ጠጅ ሞልታ ትትረፈረፋለች። |
| 11 | ልጄ ሆይ፥ የእግዚአብሔርን ተግሣጽ አትናቅ፥ በገሠጸህም ጊዜ አትመረር። |
| 12 | እግዚአብሔር የወደደውን ይገሥጻልና፥ አባት የሚወድደውን ልጁን እንደሚገሥጽ። |
| 13 | ጥበብን የሚያገኝ ሰው ምስጉን ነው፥ ማስተዋልንም ገንዘቡ የሚያደርግ |
| 14 | በወርቅና በብር ከመነገድ ይልቅ በእርስዋ መነገድ ይሻላልና። |
| 15 | ከቀይ ዕንቍም ትከብራለች፥ የተከበረም ነገር ሁሉ አይተካከላትም። |