| መጽሐፈ ምሳሌ 3 |
| 16 | በቀኝዋ ረጅም ዘመን ነው፥ በግራዋም ባለጠግነትና ክብር። |
| 17 | መንገድዋ የደስታ መንገድ ነው፥ ጎዳናዋም ሁሉ ሰላም ነው። |
| 18 | እርስዋ ለሚይዙአት የሕይወት ዛፍ ናት፥ የተመረኰዘባትም ሁሉ ምስጉን ነው። |
| 19 | እግዚአብሔር በጥበብ ምድርን መሠረተ፥ በማስተዋልም ሰማያትን አጸና። |
| 20 | በእውቀቱ ቀላያት ተቀደዱ፥ ደመናትም ጠልን ያንጠባጥባሉ። |
| 21 | ልጄ ሆይ፥ እነዚህ ከዓይኖችህ አይራቁ መልካም ጥበብንና ጥንቃቄን ጠብቅ። |
| 22 | ለነፍስህም ሕይወት ይሆናሉ፥ ለአንገትህም ሞገስ። |
| 23 | የዚያን ጊዜ መንገድህን ተማምነህ ትሄዳለህ፥ እግርህም አይሰነካከልም። |
| 24 | በተኛህ ጊዜ አትፈራም ትተኛለህ፥ እንቅልፍህም የጣፈጠ ይሆንልሃል። |
| 25 | ድንገት ከሚያስፈራ ነገር፥ ከሚመጣውም ከኃጥኣን ጥፋት አትፈራም |
| 26 | እግዚአብሔር መታመኛህ ይሆናልና፥ እግርህም እንዳይጠመድ ይጠብቅሃልና። |
| 27 | ለተቸገረው ሰው በጎ ነገርን ማድረግ አትከልክል፥ ልታደርግለት የሚቻልህ ሲሆን። |
| 28 | ወዳጅህን፦ ሂድና ተመለስ ነገ እሰጥሃለሁ አትበለው። በጎ ነገርን ማድረግ ሲቻልህ። |
| 29 | በወዳጅህ ላይ ክፉ አትሥራ፥ እርሱ ተማምኖ ከአንተ ጋር ተቀምጦ ሳለ። |
| 30 | ከሰው ጋር በከንቱ አትጣላ፥ እርሱ ክፉ ካልሠራብህ። |