| መጽሐፈ ምሳሌ 9 |
| 1 | ጥበብ ቤትዋን ሠራች፥ ሰባቱንም ምሰሶችዋን አቆመች። |
| 2 | ፍሪዳዋን አረደች፥ የወይን ጠጅዋን ደባለቀች፥ ማዕድዋን አዘጋጀች። |
| 3 | ባሪያዎችዋን ልካ በከተማይቱ ከፍተኛ ስፍራ ላይ ጠራች። |
| 4 | አላዋቂ የሆነ ወደዚህ ፈቀቅ ይበል አእምሮ የጐደላቸውንም እንዲህ አለች። |
| 5 | ኑ፥ እንጀራዬን ብሉ፥ የደባለቅሁትንም የወይን ጠጅ ጠጡ። |
| 6 | አላዋቂነትን ትታችሁ በሕይወት ኑሩ፥ በማስተዋልም መንገድ ሂዱ። |
| 7 | ፌዘኛን የሚገሥጽ ለራሱ ስድብን ይቀበላል፥ ኅጥአንም የሚዘልፍ ነውርን ያገኛል። |
| 8 | ፌዘኛን አትገሥጽ እንዳይጠላህ ጠቢብን ገሥጽ ይወድድህማል። |
| 9 | ለጠቢብ ሰው ትምህርትን ስጠው፥ ጥበብንም ያበዛል ጽድቅንም አስተምረው፥ እውቀትንም ያበዛል። |
| 10 | የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው ቅዱሱንም ማወቅ ማስተዋል ነው። |
| 11 | ዘመንህ በእኔ ይበዛልና፥ የሕይወትህም ዕድሜ ይጨመርልሃልና። |
| 12 | ጠቢብ ብትሆን ለራስህ ጠቢብ ትሆናለህ፥ ፌዘኛም ብትሆን ፌዘኛነትህን ለብቻህ ትሸከማለህ። |
| 13 | ሰነፍ ሴት ሁከተኛ ናት አሳብ የላትም፥ አንዳችም አታውቅም። |
| 14 | በቤትዋ ደጅ በከተማይቱ ከፍተኛ ስፍራ በወንበር ላይ ትቀመጣለች፥ |
| 15 | በመንገድ የሚያልፉትን አካሄዳቸውንም ያቀኑትን ለመጥራት። |