ዋና ገጽ   የመጽሐፍ ቅዱስ ቃላት መፈለጊያ   ትምህርቶች   የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች   የነጻ መዝሙሮች   ነጻ ዳውንሎድ   ያግኙን 
website search (GO!)
 
ዋና ገጽ » ጥያቄና መልስ
Email this page to a friend Printer-friendly   Sunday, 19 May 2013
ዋና ገጽ
የመጽሐፍ ቅዱስ ቃላት መፈለጊያ
የመጽሐፍ ቅዱስ ማውጫ
የዕለቱ የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ
አዮታ ሶፍትዌር
ትምህርቶች
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች
የነጻ መዝሙሮች
ነጻ ዳውንሎድ
ያግኙን Contact us
ጥያቄ መጠያየቂያ Q&A
የእገዛ ገጽ Help

ጥምቀት የአንድ ሃይማኖት ድርጅት አባል መሆንን አያሳይም ?

ሰላም የእግ/ር ቤተ-ሰዎች
1.አንድ ሰው በአንድ ሃይማኖት ድርጅት ውስጥ ቢጠመቅ (ምንም እንኳን የተጠመቀው በኢየሱስ ሰም ቢሆን) የዛ ድርጅት
አባልነቱን አያሳይም ወይ ? ይህን ያልኩት የተለያዩ ሀይማኖታዊ ድርጅቶች የተለያየ የጥምቀት ስርዓት ስላላቸው ነው!!!
2. አንድ ሰው ባይጠምቅ ደህንነት አያገኝም ? ይብራራልኝ!
11 ወራቶች በፊት መንፈሳዊ ተማሪው (120 ነጥቦች) የተጠየቀ
አመሰግናለሁ ፤የመጀመሪያው መልስ አጥጋቢ አይደለም !

2 መልሶች

0 ድምጾች
ስላም

1. የስማዮን ለምድር አንስጥ ጥምቀት ስማያዊ ነው !! የምድር የድርጅት አባል ለመሆን የድርጅቱ አባልነት ወረቀት ያስፍልጋል።

2. ደህንነት ክ አንድ አምላክ ነው በስራው የሚድን የለም። ስለዚ ደህንነት ከጥምቀት ትበልጣለች ይሕን ለመረዳት የሐዋርያት ሥራ 10፡44 አንብብ።
11 ወራቶች በፊት Henok (1,610 ነጥቦች) የተመለሰ
ወንድሜ ሄኖክ ባለው ተስማምቼ ለመጨመር ያክል ጥምቀት ወደ እግዚያብሄር መንግስት ምግቢያ ብቻ ሳይሆን በምድር ክወላጆቻችን በመወልዳችን ልጅነትን እንደተሰጠን ሁሉ በጥምቀታችን የእግዚአብሄርን ልጅነት እንዲሰጤን በ እግዚአብሄር መንፈስ እንድንወልድ መሆኑን እንድናውቅ እላለሁ የዮሐንስ ወንጌል
3፥5 ኢየሱስም መለሰ፥ እንዲህ ሲል፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም።
0 ድምጾች
ሰላም ለሁላችሁ
ለዚህ ጥያቄ ያቅሜን ያህል መልስ ለመስጠት እሞክራለሁ
በጌታ በኢየሱስ ስም እንዲህ ስል እጀምራለሁ፡፡

ስለጥምቀት የተለያዩ ሰዎች እንደየ እምነታቸው አስተምሮ የተለያዩ መልሶችን ሊሰጡበት ይችላል ፡፡ ነገር ግን ጥምቀት እንደ መፅሐፍ ቅዱስ አስተምሮ ከሆነ ትልቅ የእግዚአብሔር ሐሳብ እንደሆነ እና ለሰው ልጆች በህይወታቸው ውስጥ እጅግ አስፈላጊ የሆነ እንደሆነ እንረዳለን፡፡ በ 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3፡21 ይህም ውኃ ደግሞ ማለት ጥምቀት ምሳሌው ሆኖ አሁን ያድነናል፥ የሰውነትን እድፍ ማስወገድ አይደለም፥ ለእግዚአብሔር የበጎ ሕሊና ልመና ነው እንጂ፥ ይህም በኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ነው፤ ብሎ ሲያስታውቀን ወደ ቆላስይስ ሰዎች 2፡12 ደግሞ በጥምቀትም ከእርሱ ጋር ተቀብራችሁ፥ በጥምቀት ደግሞ፥ ከሙታን ባስነሣው በእግዚአብሔር አሠራር በማመናችሁ፥ ከእርሱ ጋር ተነሣችሁ። ወደ ሮሜ ሰዎች 6፡ 4 እንግዲህ ክርስቶስ በአብ ክብር ከሙታን እንደ ተነሣ እንዲሁ እኛም በአዲስ ሕይወት እንድንመላለስ፥ ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበርን። አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት፤ ወደ ኤፌሶን ሰዎች 4 ፡5 በነዚህና በሌሎችም ጥቅሶች ላይ የእግዚአብሔር ኃሳብ በጥምቀት በኩል ለሰው ልጆች ያለውን ኃሣብ ያስረዳናል፡፡ ስለሆነም ጠያቂው አንድ ሰው በአንድ ሃይማኖት ድርጅት ውስጥ ቢጠመቅ (ምንም እንኳን የተጠመቀው በኢየሱስ ሰም ቢሆን) የዛ ድርጅትአባልነቱን አያሳይም ወይ ? በማለት የጠየቁት ጥያቄና የእግዚአብሔር ሐሳብ በምንም መልኩ አይዛመድም የእግዚአብሔር አጀንዳ አባል የማሰባሰብ ጉዳይ ሳይሆን የኃጢአት ስርየትና የንስሐ ጉዳይ ነው ፡፡
10 ወራቶች በፊት ስም-አልባ የተመለሰ

የተዛመዱ ጥያቄዎች

1 መልስ
1 ዓመት በፊት መንፈሳዊ ስም-አልባ የተጠየቀ
3 መልሶች
5 ወራቶች በፊት መንፈሳዊ ስም-አልባ የተጠየቀ
0 መልሶች
1 መልስ
3 ሳምንታት በፊት መንፈሳዊ ስም-አልባ የተጠየቀ
የኒውስ ሌተር ምዝገባ
የእርስዎ ስም ኢሜል አድራሻዎ ኢሜል አድራሻዎ (በድጋሚ)
»የመጽሐፍ ቅዱስ ቃላት መፈለጊያ   የመጽሐፍ ቅዱስ ቃላት መፈለጊያ
Copyright © 2004-2013 by iyesus.com
Terms of use | Contact us